መካንነት በወንዶች ላይ
መካንነት የሚባለው ጥንዶች ቢያንስ ለ አንድ ዓመት ያህል ሞክረው (ቢያንስ በሳምንት 3 ጊዜ ያለወሊድ መቆጣጠሪያ) ልጅ መውለድ (ማርገዝ) ከአልቻሉ ነው። ነገር ግን ሴቷ ከ 35 ዓመት በላይ ከሆነች በ6 ወር ብቻ ምርመራ ሊጀመርላት ይችላል። በተደረገው ጥናት መሠረት 85% የሚሆኑ ጥንዶች በመጀመሪያው 12 ወር ውስጥ ሴቷ ትፀንሳለች። የተቀሩት 10% የሚሆኑት ጥንዶች ደግሞ በቀጣዩ አንድ ዓመት ውስጥ ይሳካላቸዋል። መካንነት የተለያዩ ምክንያቶች ሊኖሩት ይችላሉ። ከእነዚህ ውስጥ፤ አንድ ሦስተኛ የሚሆኑት ላይ የሴቷ ችግር፤ አንድ ሦስተኛ የሚሆኑት ላይ ደግሞ የወንዱ ችግር ሲሆን፤ የተቀሩት አንድ ሦስተኞቹ ላይ በሴቷም በወንዱም ላይ ችግር ተገኝቷል። መካንነትን በወንዶች ላይ የሚያመጡ ነገሮች ምን ምንድን ናቸው?