ህጻናት በተፈጥሯቸው አካባቢያቸውን የማወቅ ፣ የመመርመር እና የማጥናት ባህሪ አላቸው። በቤት ውስጥ ሊጎዳ የሚችሉ መድሃኒቶች ወይም ኬሚካሎች ሊያሰከሰቱ የሚችሉትን አደጋዎች ላይረዱ ይችላሉ። በስህተት በሚወሰዱ መድሀኒቶች ምክንያት በሺዎች የሚቆጠሩ ህጻናት ወደ ድንገተኛ ክፍል ይወሰዳሉ። መድሃኒቶች የአዋቂዎችን ጤንነት ለመጠበቅ የሚጠቅሙ ቢሆኑም ነገር ግን ልጆች እና በቤት ውስት የሚገኙ እንስሳት በስህተት ከወሰዷቸው ከባድ አደጋዎችን ሊያስከትሉ ይችላሉ። ልጆች ለማወቅ ካላቸው ጉጉት አካባቢያቸውን ሲያስሱ መድሀኒቶችን እንደ ከረሜላ ሊያስቧቸው እና በአጋጣሚ ሊውጡዋቸው ይችላሉ።
ለልጆች በመድሃኒት ዙሪያ ደህንነቱ የተጠበቀ አካባቢ መፍጠር አስፈላጊ ብቻ ሳይሆን ግዴታ ነው። ትክክለኛውን ማስቀመጫ መምረጥ ፣ ጥንቃቄ የተሞላባቸውን ልማዶችን ማዳበር እና የመከላከያ እርምጃዎችን ማወቅ ልጆችን በአዋቂ መድሃኒቶች ከሚያደርሱት አደገኛ ሊሆኑ ከሚችሉ ሁኔታዎች ለመጠበቅ ይረዳል። ለዚህም ነው በመድሀኒት ሽፍን ላይ ህጻናት ከማይደርሱበት ቦታ ይቀመጥ የሚል ማስጠንቀቂይ የሚሰፍረው።
በዚህ ጽሑፍ ውስጥ ደህንነቱ የተጠበቀ የመድሃኒት ማስቅመጫ ተግባራዊ ስልቶችን እንመረምራለን እና አስፈላጊ የደህንነት ልምዶችን እንነጋገራለን።
ህጻናት መድሃኒቶችን ሊወስዱ የሚችሉባቸው በርካታ ምክንያቶች ውስጥ፡-
የማወቅ ጉጉት ፡- ልጆች የማወቅ ጉጉት ያላቸው እና ብዙውን ጊዜ የሚያገኛቸውን ማንኛውንም ነገር ለመንካት፣ ለመቅመስ ወይም እንደ መጫወቻነት የመጠቀም ዝንባሌ አላቸው። በቀለማት ያሸበረቁ እና ማራኪ ሊመስሉ የሚችሉ መድሃኒቶች ከረሜላ ወይም መጫወቻዎች ሊመስላቸው ይችላሉ።
ንፁህነት ፡- ህጻናት መድሃኒቶችን እና ምንም ጉዳት የሌላቸውን እቃዎች የመለየት እውቀት የላቸውም ስለዚህም በአንድ ክኒን እና ከረሜላ መካከል ያለውን ልዩነት ላያውቁ ይችላሉ።
የእድገት ደረጃ ፡- ትናንሽ ልጆች የግንዛቤ ችሎታቸውን ሙሉ በሙሉ አልዳበረም, ይህም ማለት ድርጊታቸው የሚያስከትለውን መዘዝ ላይረዱ ይችላሉ። እንዲሁም መድሃኒቶች ሊያስከትሉ የሚችሉትን ጉዳት አይረዱም።
አዲስ ነገርን ፍለጋ ፡- ልጆች ቦርሳዎችን, ካቢኔቶችን ማሰስ ተፈትሮዊ ባህሪያቸው ነው። ምንም እንኳን መድሃኒቶች ሊደርሱበት የማይችሉ ናቸው ብለው ቢያስቡም ልጆች እነሱን ለማግኘት መንገድ ይፈልጋሉ።
የተገደበ ራስን መግዛት፡- ልጆች ብዙውን ጊዜ ነገሮችን ወደ አፋቸው ለማስገባት ራሳቸውን የመግዛት እና የመቆጣጠር አቅም የላቸውም ስለዚህም ሲጫወቱ ወይም ሲመራመሩ በአጋጣሚ መድሃኒት ወደ አፍቸው ሊከቱ ይችላሉ።
መድሃኒቱን ሁል ጊዜ ከልጆች ርቆ እንዲቆይ ለማድረግ ትኩረት መስጠት አስፈላጊ ነው።
ለምንድነው የልጆችን ደህንነት በመድሃኒት ዙሪያ መጠበቅ አስፈላጊ የሆነው?
በተለይ ህጻናት ባልጠነከረ እና ባልዳበረ የሰውነት አካል ክፍሎች ምክንያት የአዋቂዎች መድሃኒቶች ሊጎዷቸው ይችላል። ለዚህ ነው ተጨማሪ ጥንቃቄ ወሳኝ የሆነው፡-
አደገኛ እና መርዛማ ተፅዕኖዎች፦ ለአዋቂዎች ደህንነቱ የተጠበቀ አንድ መድኃኒት ለልጆች ግን መርዛማ እና አልፎ ተርፎም ህይወትን የሚያሳጣ ሊሆን ይችላል።
ማራኪ መልክ፡- ደማቅ ቀለም ያላቸው እንክብሎች ከረሜላ ሊመስሉ ይችላሉ፣ እና ጣፋጭ ጣዕም ያላቸው ፈሳሽ መድሃኒቶች ለልጆች ጭማቂ ሊመስሉ ይችላሉ።
ተፈጥሯዊ የማወቅ ጉጉት፡- ልጆች አካባቢያቸውን ይመረምራሉ እና ብዙ ጊዜ ነገሮችን ወደ አፋቸው ያስቀምጣሉ፣ ይህም በአጋጣሚ ወደ አፋቸው የመክተትን እድልን ይጨምራል።
ልጆችን ከመድሃኒቶች ለማራቅ የሚረዱ ጠቃሚ ምክሮች፡-
መድሃኒቶችን ከልጆች ለመጠበቅ ውጤታማ ጥንቃቄዎችን ማድረግ አስፈላጊ ነው።ልጆችን ከመድሃኒቶች እና ከሚጎዳቸው ነገሮች ለመጠበቅ ወላጆች እና ተንከባካቢዎች የሚከተሉትን ጨምሮ የደህንነት እርምጃዎችን መተግበር አስፈላጊ ነው፡-
- መድሃኒቶችን መቆለፍ ወይም በማይደረስበት ቦታ ማስቅመጥ:- በሐኪም የታዘዙ እና ከሀኪም ትእዛዝ ውጭ ያሉ መድሃኒቶችን ቪታሚኖችን ጨምሮ ህጻናት በቀላሉ ሊደርሱበት በማይችሉበት ቦታ፣ ከፍታ ባላቸው መደርደሪያዎች እና በተዘጋ ካቢኔት ውስጥ መቀመጥ አለባቸው።ሁል ጊዜ መድሃኒቶችን እና ቫይታሚኖችን ከተጠቀሙ በኋላ ወዲያውኑ ሊገኙበት ወደ ማይችልበት ቦታቸው መመለስ። የልጆች መድሃኒት. ለማንኛውም ተንከባካቢዎች ለልጅዎ መድሃኒቶች ግልጽ መመሪያዎችን ይጻፉ.
- ማስተማር፡- ልጆችን በመድኃኒት እና ከረሜላ መካከል ስላለው ልዩነት ማስተማር እንዲሁም ሊከሰቱ የሚችሉትን አደጋዎች ማብራራት እና አዋቂዎች ብቻ መድሃኒቶችን መያዝ እንዳለባቸው አጽንኦት ሰጥቶ መንገር አስፈላጊ ነው። ልጆችን ገና በልጅነታቸው ስለ መድሃኒት ማስተማር መጀመር ወሳኝ ነው። መድሃኒት ጠቃሚ እና ደህንነቱ የተጠበቀ ሊሆን ይችላል ይሁን እንጂ በዛውም ልክ መድሐኒት ሰውነትን በእጅጉ ሊጎዳ አልፎ ተርፎም የሰውነትን ሥራው ሊያቆም እንደሚችልም ማሳሰብ።
- ወላጅ ካልሰጣቸው በስተቀር ልጆች በፍጹም መድሃኒት መውሰድ፤ መያዝ፤ እንዲሁም መጫወት የለባቸውም የሚለውን መልእክት ማሳሰብ።
- የመድሃኒት ሽፋንን ወይም በመድሃኒት ጠርሙሶች ላይ ያሉ መክደኛዎች በተጠበቀ ሁኔታ መቆለፉን ሁልጊዜ ማረጋገጥ ያስፈልጋል።
- ኃላፊነት እንዲሰማቸው ፤ ራሳቸውን መንከባከብ እንዲችሉ ማበረታት፡ ልጆች እያደጉ ሲሄዱ ቀስ በቀስ የራሳቸውን መድሃኒት እንዲቆጣጠሩ ማስተማር። ይህም ትክክለኛውን መጠን እንዴት እንደሚጠቀሙ ማወቅ እና መድሃኒትን ደህንነቱ በተጠበቀ ሁኔታ ማስቀመጥን ይጨምራል። መድሃኒቱ ጥሩ ጣዕም ስላለው ወይም ለመውሰድ ብቻ ሳይሆን አስፈላጊ በሚሆንበት ጊዜ ብቻ መውሰድን ያካትታል።
- መለያዎችን ማንበብ ፡- ሁልጊዜ መለያዎችን ማንበብ እና የመድኃኒት መመሪያዎችን በጥንቃቄ መመልከት። በልጆች ፊት አዘውትሮ መድሃኒት ከመውሰድ መቆጠብ ባህሪውን እንዳይኮርጁ ይረዳል።
- በአግባቡ ማስወገድ፡- ጥቅም ላይ ያልዋሉ ወይም የዋሉ ፣ የማያስፈልጉ እና ጊዜ ያለፈባቸውን መድሃኒቶችን በአግባቡ እና በተገቢው መንገድ ማስወገድ።
- የአደጋ ጊዜ ቁጥሮችን መያዝ ፡- በአደጋ ጊዜ በፍጥነት ወደነዚህ ቁጥሮች መደወል እንዲያስችል የአደጋ ጊዜ ቁጥሮችን መያዝ አስፈላጊ ነው።
- ክትትል:- ሁልጊዜ ልጆችን በተለይም ጎጂ ሊሆኑ ከሚችሉ ነገሮች ዙሪያ መጠበቅ
- እንዲሁም ከታመመ ህጻናት አጠገብ መድሃኒትን አርቆ ማስቀመጥ ያለ ክትትልም አለመተዉ።




